Blue Joomla Templates

Visitors Counter

mod_vvisit_countermod_vvisit_countermod_vvisit_countermod_vvisit_countermod_vvisit_countermod_vvisit_counter
mod_vvisit_counterToday53
mod_vvisit_counterYesterday46
mod_vvisit_counterThis week53
mod_vvisit_counterLast week175
mod_vvisit_counterThis month811
mod_vvisit_counterLast month1300
mod_vvisit_counterAll days14725

We have: 41 guests online
Your IP: 3.128.198.172
Mozilla 5.0, 
Today: Jun 30, 2024

Vinaora World Time Clock

Online User

We have 41 guests online

Archieved Content

PDF Print E-mail

የወረዳዉ ማህበረሰብ ባህላዊ እሴቶችና የመስህብ ሀብቶች

ባህል የአንድን ማህበረሰብ የአኗኗር ዘይቤ ፣አስተሳሰብና በአንድ ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ አዉድ ዉስጥ ያለዉን ልምድና ባህሪ የሚገልጽ በአጠቃላይ ቁሳዊና ህሊናዊ ሀብቶቹን የሚያካትት ሰፊ ጽንሰ ሀሳብ እንደሆነ በርካታ የዘርፉ ምሁራን ይስማሙበታል፡፡ የኢፌዲሪ መንግስት ጥቅምት 1990 ዓ.ም ባወጣዉ የባህል ፖሊሲ በገጽ 5 ላይ ስለ ባህል የሚከተላዉን ያስቀምጣል ፡፡

«..ባህል የሰዉ ልጅ ሰብዓዊና ምክንያታዊ ፍጡር እንዲሆን ያስቻሉት ወይም ከሌሎች ፍጡራን ለመለየት ያበቁት ማንኛዎቹም ምሁራዊ ስነ ምግባራዊ ፣አካላዊ ፣ቴክኒካዊና በአዕምሮ እዉቀት ራሱን የማሰልጠን ሁኔታዎች የሚያጠቃልል ጽንስ ሀሳብ ነዉ፡፡ እንዲሁም አንድ ህዝብ ከሌላዉ ተለይቶ የሚታወቅባቸዉን ሁኔታዎች ማለትም የአኗኗር ዘይቤዎቹን ፣እምነቶቹን ትዉፊቶቹን ፣በአጠቃላይ ቁሳዊና ህሊናዊ ሀብቶቹን የሚያካትት ሰፊ ጽንስ ሀሳብ ነዉ፡፡» የሚል ነዉ፡፡

ይሄ ትርጓሜ ከወረዳዉ ብሔረሰቦችና ህዝቦች አንጻር ሲታይ የእነዚህ የባህል ሀብቶች ባለቤት ሲሆን አንዳቸዉ ከአንዳቸዉ የሚለዩበትን ማህበራዊና፣ኢኮኖሚያዊ ፣ፖለቲካዊ ፣አስተዳደራዊ /ህጋዊ/ ስነ ምግባራዊ ሀይማኖታዊና ስነ ልቦናዊ ሁኔታዎችን ወይም ቋንቋዎቻቸዉን፣ታሪክና ስነ ቃሎቻቸዉን ፣ቤት አሰራራቸዉን ፣የማምረቻ መሳሪያዎቻቸዉንና አመጋገባቸዉን ፣ልብስና አለባበሳቸውን፣አጋጊያጣቸውንና የስነ ውበት ግንዛቤያቸውን ፣ሀይማኖታዊና የእምነት ክንዋኔዎቻቸዉን፣ ከወሊድ ከሠርግና ከሞት ጋር የተያያዙ ስርዓቶቻቸዉን ፣በዝምድና በጉርብትናና በሌሎች ግንኙነታቸዉ ላይ የተመሰረተ መተጋገዝና መተሳሰባቸዉን፣ባህላዊ የአስተዳደር ዘይቤያቸዉን ፣ባህላዊ የጤና እንክብካቤ ዘዴዎቻቸዉና ሌሎችንም ሁሉ የሚያጠቃልል ነዉ፡፡ እንዲሁም የወረዳዉን ህዝቦች ቅርሶች ፣ስነ ጥበባትና ዕደ ጥበባት ፣ልዩ ልዩ ትዉፊቶች ፣ጭፈራ ፣ዉዝዋዜና ዘፈኖቻቸዉ ፣ንግድ ትምህርት በብሔረሰቦቹ የሚከበሩ ባህላዊና ሀይማኖታዊ ክብረ በዓላትና ባህላዊ ትዕይንቶች ይካተታሉ፡፡

እነዚህን የወረዳዉን ህዝቦች የተለያዩ የባህል እሴቶች ቁሳዊና መንፈሳዊ የባህል ዕሴቶች በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ከፍለን ማየት ይቻላል፡፡ የወረዳዉን ህዝብ ቁሳዊ ባህል ሲባል የሚታዩ ነገሮች ፣መገልገያ መሳሪያዎችን ፣ግንቦችን/ልዩ ልዩ የቤት አሠራሮችን/፣ታሪካዊ እቃዎችን እና ቦታዎችን ወዘተ.. የሚያካትት ሲሆን መንፈሳዊ ባህል ሲባል ደግሞ ፖለቲካዉን ፣ሙዚቃቸዉን፣ግጥሙን ፣ትምህርቱን ፣ሃይማኖቱን ፣ወጎቹንና ልማዶቹን ወዘተ… የሚያካትት ነዉ፡፡ እነዚህ የወረዳ ህዝብ ሀብቶች ከትዉልድ ትዉልድ ሲተላለፉ የኖሩ አሁንም፣ በመተላለፍ ላይ ያሉ ህዝቡ በተለያየ ጉዳዮችና ነገሮች የተለየ ስያሜ በመመስረት በስምምነት የሚግባባቸዉና የሚጠቀምባዉ ሀብቶች ናቸዉ፡፡

ከዚህ በመነሳትም የአርጡማ ፉርሲ ወረዳ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ከሌላዉ የሚለዩበት ፣ዝንባሌያቸዉን ፣ባህሪያቸዉን እና የህዝቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያስተካክሉበት እና ተፅዕኖ የሚያሳርፉበት የራሳቸዉ የሆነ የተለየ ባህል አላቸዉ፡፡ የወረዳዉ ህዝብ የእነዚህ ከላይ ቁሳዊና መንፈሳዊ ባህሎች በማለት የተገለፁት የባህል ዕሴቶች ባለቤት ሲሆን ህዝቡ እነዚህን ባህሎች የሚያከናዉንበት የራሱ ታሪካዊና ባላዊ የአከዋወን ስርዓት አለዉ፡፡

እነዚህን የተለያዩ ባህላዊ እሴቶች ስናይ ከቀበሌ ቀበሌ የሚለያዩና ሁሉም ባህላዊ እሴቶችና መስህቦች የወረዳዉን ህ/ሰብ አኗኗር ስርዓቱን ፣ማንነት ፣የህዝቡን ጥበብ ፣የሰዉ ልጅ ላይ መልሶ እንዲያንፀባርቅ የማድረግ ችሎታቸዉን የሚያሳዉቁበትና ሰዉ በስብዕናዉ የተሟላ መሆኑን የሚያዉቁበትን ፣ህዝቡ በማህበራዊ ህይወቱ አግባብ ባለዉ አስተያየት ፍርድ የሚሰጥበትን /የአበጋር የባህላችን ዳኝነት ስርዓት/ አግባብ፣ ከሌሎች ህዝቦችና የጎረቤት አከባቢያቸዉ ጋር ያለዉን ባህላዊ ትስስርና ማህበራዊ ግንኙነት ምን እንደሚመስል በትክክል የሚገልጹ ናቸዉ፡፡

እነዚህ የወረዳዉ ህዝብ የባህል እሴቶችና ሀብቶች ለልማት ካላቸዉ አጋዥነት አንዱ የቱሪዝምን እድገት እንቅስቃሴና በርካታ የቱሪዝም ሀብቶችን በማሰስ ፣በማጥናትና በማስተዋወቅ የቱሪስት ፍሰትን ቁጥር በመጨመር ወረዳዉ ከቱሪዝም እንዱስትሪ ተጠቃሚ እነዲሆን በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ሚና መጫወት ይችላሉ፡፡

በተጨማሪም እነዚህ የወረዳዉ ባህላዊ ሀብቶች /ባህላዊ አለባበስና አጋጊያጥ ፣ባህላዊና ሀይማኖታዊ ክብረ በዓላት ፣ባህላዊ ክንዋኔዎች ማለትም የአበጋር የዳኝነት ስርዓት ፣ቦለቀያ የሴቶች የዉበት ሳሎን ፣የባህላዊ ምግቦች አመጋገብ ፣ባህላዊ የቤት አሰራር ፣ባህላዊ የመገልገያ ቁሳቁሶች ወይም የዕደ ጥበብ ዉጤቶች ፣ባህላዊ ዘፈኖች፣ጭፈራዎችና ባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያዎች /ማህበራዊ ግንኙነትና ትስስር መግለጫ አዉዶች /ሠርግ ለቅሶ /፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መረዳጃ ተቋማት ኪነ ጥበብ ለወረዳዉ የገጽታ ግንባታ አንዱና ዋነኛ ታሪካዊ የባህል መግለጫዎች ናቸዉ፡፡ ከነዚህ ሀብቶች ወረዳዉ ጭስ አልባ እንዱስትሪ በመባል ከሚጠራዉ የዘመናችን የቱሪዝም እንዱስትሪ ከፍተኛ ገቢ ማግኘት ሲችል አሁን ካለዉ ነባራዊ ሁኔታ ግን ከዘርፉ የሚገኘዉ ገቢ ዝቅተኛ ነዉ፡፡ ስለሆነም እነዚህን የወረዳዉን ታሪካዊና ባህላዊ የመስህብ ሀብቶችን ትኩረት ሰጥቶ በማልማት ረገድ ገና ሰፊና ትልቅ ጥረትን የሚጠይቅ የወረዳዉ ህዝብና የመንግስት አካላት የወደፊት የቤት ስራ ናቸው ፡፡ እነዚህን ከላይ ያየናቸውን የወረዳዉ ባህላዊ እሴቶችና የመስህብ ሀብቶች የሚከወኑበትንና ባህላዊ የአከዋወን ስርዓት ከዚህ በታች እንደሚከተለው ዘርዘር በማድረግ ለማቅረብ ተሞክሯል ፡፡

1. የዕደጥበብ ውጤቶችና ባህላዊ መገልገያ ዕቃዎች

የወረዳዉ ብሄረሰቦች የራሳቸውን የፈጠራ ችሎታ የሚለኩና ልዩ የሚያደርጓቸውን በርካታ ቁሶችን አምርተው የመጠቀም ልምድ አላቸው ፡፡ በዚህም የተነሳ ወረዳዉ በርካታ የእደጥበብ ሀብቶች ባለቤት ነው፡፡ ከነዚህም መካከል የሽመና እና የዕደ ጥበብ ስራ ዉጠቶች ይጠቀሳሉ፡፡ የረጅም ጊዜ ዕድሜ ያላቸዉ የጥበብ ስራዎች የፈጠራ ባለቤት አሁን ለደረሰበት የእድገት ደረጃ የራሳቸዉን አስተዋጽኦ ያበረከቱ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለዉም፡፡ ምክንያቱም ጥናትና ምርምር /የፈጠራ ስራ/ የሚጀምረዉ ባህላዊ ልምድን መሰረት አድርጎ በመሆኑ ነዉ፡፡ እነዚህ የፈጠራ የመገልገያ ዕቃዎች የህዝቡን የማህበራዊ ግንኙነት ፣ፖለቲካዊ ግቡን ፣የንግዱን ዘርፍ ፣የግብርና ዘርፍ ወዘተ.. ሊገልጹ የሚችሉ የማንነቱ መገለጫዎች ናቸዉ፡፡ ከነዚህ መካከል የሚከተሉት ዋና ዋናዎቹን ዝርዝር በማቅረብ ከምን እንደሚሰሩና ለምን ጥቅም እንደሚዉሉ እናስቀምጣለን፡፡

ሀ. ከእንጨት የተሰሩ

  • · ብርኩማ ፡- ከዕንጨት የተሰራ ሆኖ ለገጠር ሴት ትራስነት የሚያገለግል ሲሆን የብሐሀረሰቡ ልጃገረዶች ሲዳሩ ወደ አዲሱ ጎጆአቸዉ ይዘዋቸዉ ከሚሄዷቸዉ የቤት ቁሳቁሶች መካከል አንዱ ነዉ፡፡ ቅርፁ እንደ ኮርቻ በግራና በቀኝ ከፍ ያለና ከስር መሃሉ የጎደጎደ ሲሆን ዉስጡ እንደ ሙቀጫ ክፍት የሆነ መቀመጫ አለዉ፡፡ በዉስጡ የፀጉር ቅቤ ለማስቀመጥ ይጠቀሙበታል፡፡
  • · ናርጂ /ከዕንጨት የተሰራ ባህላዊ ቅቤ መያዢያ/
  • ·ቆሪ፡- ከእንጨት የሚሰራ ከላይ ዉስጡ እንደ ሙቀጫ የጎደጎደ ሲሆን ለወጥ፣ለገንፎ፣ለወተትና ለጥራጥሬ ማቅረቢያነት ያገልግላል፡፡
  • ·ድቤ /ከበሮ/፡- ከእንጨት የሚሰራና እንደ ቆሪ ከላይ ዉስጡ የጎደጎደ ሲሆን ከላዩ ላይ በቆዳ የተሸፈነ በወዳያ ጊዜ ይጠቀሙበታል፣
  • · ኩርሲ /የቁርዓን ማስቀመጫ ለማንበብ/
  • ·ቆቲ እንደ ዱላ ረዘም ያለ ከእንደት የሚሰራ ሆኖ ሽማግሌዎች በወዳያ፣እጮኛ ለማጨት ሲሄዱ፣በሰርግ ወዘተ ጊዜ እንደ ዱላ የሚጠቀሙበት የብሔረሰቡ ባህል ነዉ፡፡

ለ. ከብረታ ብረት የተሰሩ

  • ጊሌ ፡- እንደ ሴንጢ ከብረት የሚሰራና ዙሪያዉን በቆዳ ተሸፍኖ ሰዎች እንደ ጌጥነት፣ በእርድ ጊዜ፣ በበዓል ወቅት፣ በዝግጅትና ገበያ ሲወርዱ ወገባቸዉ ላይ በድልግም ላይ ይታጠቁታል፣
  • · ጩቤ ከጊሌ ጋር ተመሳሳይ ሆኖ ርዥመቱ አነስተኛ ናት፣
  • · የእንጨት ማበጠሪያ
  • · የእንጨት ማንኪያ
  • · ጭልፋ
  • · ሳህን
  • · ማንኪያ
  • · በራድ /እብሪቅ/
  • · ብረት ድስት
  • · ወስፌ


ሐ. ከቆዳ የተሰሩ

  • · ቀርበታ ከከቆዳ የሚሰራ ሆኖ ዱሮ ጃሪካን በሌለበት ወቅት ለዉሃ መቅጂያነት የሚያገልግል ነዉ፣
  • · ሳጳና --በዛጎል ያጌጠ የግድግዳ ጌጥ ነዉ እንዲሁም ልጅ ለማዘልም ይጠቀሙበታል፣

መ. ከቅልና ከስፌት እቃዎች የተሰሩ.

  • · ኦኮሌ ቅል ሆኖ በቆዳ የተጌጠና ማንጠልጠያ የተበጀለት የወተት ማለቢያነት ያገለግላል፣
  • · ሞሶብ ወርቅ በሰርግ ወቅት የሚቀርብና የሳሎን ጌጥ የሆነ የስፌት ዕቃበ ነዉ፣
  • · ሙዳይ --አገልግል መሰል የሴቶች ጌጣጌጥ ማስቀመጫነት የሚያገለግል የስፌት ዕቃ ነዉ፣
  • · ወስከንባይ -- በገጠር ለጥራጥሬና ምግብ ማቅረቢያና ለግድግዳ ጌጥ የሚያገለግል የስፌት ዕቃ ነዉ፣
  • · አገልግል ሰዎች እርሻ፣መንገድ፣ሰዎችን ለመጠየቅ ሲሄዱ እንጀራ የሚያቅሱበት ክዳኑና እናቱ በቆዳ የተሸፈነ የስፌት እቃ ነዉ፣

 

2.  ባህላዊ አለባበስና አጋጊያጥ

የወረዳዉ ማህበረሰብ የራሱ የሆነ ዉብና ማራኪ የአለባበስና አጋጊያጥ ስርዓት አለዉ፡፡ በተለይ በወረዳዉ ዉስጥ ከሁለት በላይ ብሔረሰቦች መኖር የእነዚህን ህዝቦች የተለያዩ ዓይነት አለባበስና አጋጊያጥ በቀላሉ ለማየት ያስችለናል፡፡ በተለይ በወረዳዉ ዉስጥ በሚገኙ ዋና ዋና የገበያ ቦታዎች በገበያ ቀን ለአብነትም ያህል በጨፋ ሮቢት፣በአርጡማና በበኬጃ የገበያ ቦታዎች ብቅ ቢሉ የእነዚህን ብሔረሰቦች ማለትም የኦሮሞ፣አማራንና አፋር ልጃገረድን ፣ኮበሌ/ወጣት ወንድ/ ፣ የአዋቂ ወንድ ፣ያገባች ሴት ፣የዱበርቲ/የአዋቂ ሴት/ የአለባበስ ስርዓቶችንና የሁሉም ብሔረሰቦች የጌጥ አጋጊያጥ ማየት ይችላሉ፡፡ ይሄ ዓይነቱ ትዕይንት ህብር ፈጥሮ የህብረተሰቡን ዉብ ባህላዊ አለባበስና አጋጊያጥ ስርዓትና ህ/ሰቡ ስለ ስነ ዉበት ያለዉን ግንዛቤ ስለሚያሳየን ህሊናችን ተመስጦ ዉበትን እንዲያደንቅ ስሜታችንን ይገዙታል፡:

የወረዳዉ ማህበረሰብ በሽመና የተሠሩ የባህል ልብሶችንና የዕደ ጥበብ ዉጤት የሆኑ ጌጣጌጦችን አምርቶ በስፋት የመጠቀም ልምድን ያካበተ ህዝብ ነዉ፡፡ ህብረተሰቡ ራሱ አምርቶ ስለሚጠቀምባቸዉ ከህፃን እስከ አዋቂ ባህላዊ አልባሳትንና ጌጣጌጦችን አዘዉትሮ ሲጠቀም ማየት የተለመደ ነዉ፡፡

 

2.1 በዋናነት የሚታወቁ ባህላዊ አልባሳት

የወንድ ባህላዊ አልባሳት

  • · ጉሮ፡- በሽመና ከጥጥ የሚሰራና የተሰፋ ሸሚዝ መሰል ወንዶች ከላይ የሚለብሱት ነው፣
  • · ሻል፡- በተለያዩ የክር ቀለማት ያጌጠና ከሱፍ መሰል ነገሮች የተሰራ ለፍራሽና አልጋ ልብስነት ፣እንደ ፎጣ

የሚለበስ ለስጦታ የሚሆን አገልግሎት አለዉ፡፡ በተለይ ወንዶች በወጣትነት ጊዜያቸዉ በእንግድነት በሚድሩበት ቦታ ላይ እንደ ሌሊት ልብስነትም ይለገሉበታል፣

  • · ዲጌ/ሰበታ/፡- ከሁለቱም ጫፍ በጥለት ክር ያሸበረቀ ነዉ፡፡ዲጌን በአማርኛ መቀነት ይሉታል፡፡ የሴቷ ርዝመቱ ከ1- 1.5 ሜትር ሲሆን የወንዱ ደግሞ ከ2-3.5 ሜትር ይደርሳል፡፡
  • · የወንድ ሽርጥ/አሳ በረንዳ/፡- ዉድ የሆ የፋብሪካ ዉጤት ነዉ፡፡ በህዝቡ ዘንድ በብዛት ተዘዉትሮ ይለበሳል፡፡
  • · መስነፍ፡ - በሽመና ከጥጥ የተሰራ ወንዶች የሚያሸርጡት ዉድ ልብስ ነዉ፡፡ ለስጦታ የሚቀርብ ዉብትና ማራኪ

ነዉ፡፡ በበዓል ቀናት፣በዝግጅት ቀናች እና በገበያ ቀናቶች ተዘዉትሮ ይለበሳል፡፡

የሴቶች ባህላዊ አልባሳት

  • · ወንደቤ፡- ወንደቤ በሽመና ከጥጥ የተሰራ የወንድና የሴት ልብስ ነዉ፡፡በባቲ አካባቢ ህ/ሰቡ ልብሱን ቅቤ በመንከር

ይጠቀምበታል፡፡

  • · ጥልፍ ቀሚስ፡ - በተለያዩ የጥልፍ ዲዛይኖች የተንቆጠቆጠ የሴቶች ሙሉ ልብስ ነዉ፡፡
  • · የሀር ሽርጥ፡- ብዙዉን ጊዜ ልጃገረዶች የሚያሸርጡት ልብስ ነዉ፡፡ 100% ከሀር የተሰራም ነዉ፡፡ ሌላ ስሙ ደግሞ ዳንጉሳ ይባላል፡፡
  • · ጨፌ/ጃኖ/፡- በሽመና ከጥጥ የተሰራ በአከባቢዉ ሴቶች የሚለበስ የሴቶች ሽርጥ ነዉ፡፡ ከታች ሰፊ ጥለት አለዉ፡፡
  • · የወገብ መቀነት፡- ርዝመቱ ከ1-1.5 ሜትር ሆኖ ከሽመና የሚሠራ በሁለቱም ጫፎች ላይ በተለያዩ ቀለማት ያሸበረቀ የሴቶች የወገብ መቀነት ነዉ፡፡

3. ሀይማታዊ አልባሳት

1. በአካባቢዉ በሙስሊሙ ህ/ሰብ ዘንድ እንደ ጀለቢያ ፣ጥምጣም፣ቆብ የወንዶች አልባሳት ሲሆኑ ሂጃብ፣ጅልባብ፣ኒቃብ የሚታወቁ ሀይማኖታዊ የሴቶች አልባሳት ናቸዉ፡፡

2. በአካባቢዉ ክርስቲያን ህ/ሰብ ዘንድ የወንድ ካፖርት ፣አክሊል ፣ቀሚስ ፣ቆብ፣ የሽመና ልብሶች /የሴት ጥበብ…/ የሚታወቁ መንፈሳዊ አልባሳት ናቸዉ፡፡

4. ባህላዊ ጌጣጌጦች

የወንድ ጌጣጌጦችና ጥቅሞቻቸው

  • · ሂንቴ(ባሩድ)፡- ልዩ ልዩ ቀለማት ባሉት የፕላስቲክ ዉጤት ተሰርቶ ግንባር ላይ የሚታሰር ጌጥ ነዉ፡፡

በተጨማሪም ለወጣት ወንዶች የአንገት ለልጃገረዶች ደግሞ የጸጉር ጌጥ ሆኖ ያገለግላል፡፡ አጠቃቀሙም የተለያዩ ቀለማት ያሉት ፕላስቲኮች በትንሹ በመቀቆራረጥ ወይም የጥይት እርሳሶችን በክር ላይ በማሰር አንገት ላይ ለዉበትነት ይታሰራል፡፡

  • · ቸብቸብ(ጃቢ) ፡-ከመርፌ ቁልፍ ጋር በተለያዩ ቀለማት ካላቸዉ የጥለት ክሮች ተሰርቶ ወጣቶች በደረታቸዉ ላይ በመርፌ ቁልፉ በማሰር ያጌጡታል፡፡
  • · ጊሌ፡- ከብረት የሚሠራ የወንድ ጌጥ ነዉ፡፡

የሴት ጌጣጌጦችና ጥቅሞቻቸው

  • · የፀጉር ጌጥ /ፈሰሴ/ ፡- አንድ ልጃ ገረድ ከ14 አመት በኋላ ፈሰሴን መጠቀም ትችላለች፡፡ ካገባችም በኋላ እስከ ምትወልድ ድረስ መጠቀም ትችላለች፡፡ ከ ሀርም ሆነ ከነሀስ መሠራት ይችላል፡፡
  • · የጆሮ ጌጥ /ሎቲ/ ፡- መጠሪያ ስሙ እንጭልጭሌ ሲሆን ስድስት የሚንጠለጠል ነገር ስላለው ወይም ስለሚቅጨለጨል ስሙ እንጭልጭሌ ወይም ጀሄ ተብሎ ይታወቃል፡፡ ይሄ የሚገዛው በእጮኛ ነው፡፡ ከብርም ሆነ ከነሃስ የሚሰራ ነው፡፡ ሶስት እንጥልጥል ያለው ደግሞ አንዲት ልጃ ገረድ ከመታጨቷ በፊት ጆሮዋን እንደተበሳች የምታጌጥበት እንጭልጭሌ ነው፡፡ ልክ እንደተ ታጨች ደግሞ ባለ ስድስቱን እንጭልጭሌ ታጌጣለች፡፡
  • · የአንገት ጌጥ /ብረብስ/ ፡- ልጃ ገረዶች ከመታጨታቸው በፊት አንድ ፍሬ ብረብስ አንገታቸው ላይ ያደርጋሉ፡፡ ልክ ለመታጨት ሲደርሱ ደግሞ ሁለት ያደረጋሉ፡፡ እንደታጩ ደግሞ ሶስት ፍሬ አንገታቸው ላይ ያደርጋሉ፡፡ የሚሰራው ከብር ወይም ከማሪያ ቲሬዛ ሳንቲም ነው፡፡
  • · ጎሃ ፡- ያገባችም ሆነ ያላገባች ሴት ማጌጥ ትችላለች፡፡ ጀግና ባል/ቤተሰብ ያላት ሴት በዚህ ማጌጥ ትችላለች፡፡ ጎሃን ያጌጠች ሴት የጀግና ሚስት ወይም የባላባት ቤተሰብ መሆኑዋ ይታወቃል፡፡ የሚሰራው ከብርም ሆነ ከነሐስ መሰራት ይችላል፡፡ ጎሃው ላይ የተንጠለጠሉት ጌጦች ውለዱ ክበዱ የሚል ተስፋ ያለው መልዕክት ያስተላልፋሉ፡፡ እጮኛ ወይም ባል ጀግና ከሆነ /ባላባት ከሆነ ነው ገዝቶ የሚያጌጣት፡፡
  • · ነጭ ቀበቶ /ቶርቢ/ ፡- እጮኛዋ የሚገዛላት ስጦታ ነው፡፡ ቶርቢ የተባለው ከኦሮምኛ ቃል የተወሰደና በአብዛኛው የአከባቢው ኦሮሞዎች የሚጠቀሙበት ስለሆነ ትርጉሙም ሰባት የተለያዩ ጌጣጌጦች ስላለው ቶርቢ ተባለ፡፡ ቶርቢ ማለትም በኦሮምኛ ሰባት ማለት ነው፡፡ እጮኛው ይሄንን ስጦታ ሲያመጣ ቤተሰቦቿ ተቀብለው እናቷ ወይም አክስቷ ልጃ ገረዷን ያጌጣሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ይሄንን ጌጥ ካረገች እጮኛ አለኘ የሚል መልዕክት ታስተላልፋለች፡፡ አንድ ልጃ ገረድ ከታጨች በኋላ ከብቶች አታግድም፡፡ ገበያ ስትወርድ ፣ውሃ ስትቀዳ፣ሠርግ ስትሄድ ጌጡን ትጠቀመዋለች፡፡ ካገባች በኋላ ግን ጌጡን ማጥለቅ አትችልም፡፡ ምክንያቱም ያገባች ሴት በቶርቢዉ ምትክ የወገብ መቀነት ከሽመና የተሠራ የምታስረዉ ጌጥ ስላለ ነዉ፡፡
  • · ጉሜ/ግጥሞሽ/አንባር/ ፡- ይሄ ጌጥ ከታጨች በኋላ ወደ ሰርግ ፣ገበያ ወዘተ ስተሄድ እጆቿ ላይ ታጌጣለች፡፡ ከወንድ አጮኛ የሚበረከት ነዉ፡፡ የታጩ ልጃገረዶች እንደ መለያ የሚያገለግል ለከብር የተሠራ ጌጥ ነዉ፡፡
  • · ተሙኒ፡- ከብርና ከነሃስ የተሰራ በአንድ ገጽ የሰዉ ምስል ያለበትሲሆን በስተጀርባዉ ገጹ የአንበሳ ምስል ያለዉ ሳንቲም የክር ማንጠልጠያ ቀዳዳ ተበጅቶለት በአንገታቸዉ ላይ በማንጠልጠ ያጌጡታል፡፡
  • · አልቦ፡- ያገባች ሴት የምትጠቀመዉ የእግር ጌጥ ነዉ፡፡ ከብር የተሰሩ ቁርጥራጭና ዝርግ አልቦዎች ሁነዉ በበዓል ቀን፣በሠርግ ቀናቶች፣ እና ከቤቷ ወጣ በምትልበት ያገባች ሴት የእግር ዉበቷን ለመጠበቅ ሲባል የሚጌጥ ጌጥ ነዉ፡፡ በተለይ በእግሯ ላይ ሂና ስለምታስር አልቦዉን ስታጠልቅ ደግሞ የበለጠ ያሳምረዋል፡፡
  • · የግንባር ጌጥ /ሂንቴ/ ፡- ልዩ ልዩ ቀለማት ባሉት የፕላስቲክ ዉጤት ተሰርቶ ግንባር ላይ የሚታሰር ጌጥ ነዉ፡፡ በተጨማሪም ለወጣት ወንዶች የአንገት ጌጥ ለልጃገረዶች ደግሞ የግንባር ጌጥ ሆኖ ያገለግላል፡፡
 
free pokerfree poker

Slide Show

LOADING
Photo Title 1Photo Title 2Photo Title 3Photo Title 4Photo Title 5
JT-SlideShow-Footer

About Our delivery

About Our delivery
 

Artumafursi Copyright© 2009 All Rights Reserved.

Designed by Artumafursi Woreda ICT Core Process